1. ወደ ይዘቱ እለፍ
  2. ወደ ዋናዉ ገጽ እለፍ
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ እለፍ

የተፈናቃዮች የአዲስ ዓመት ምኞትና ተስፋ

ዓለምነው መኮንን
ሐሙስ፣ መስከረም 1 2018

ከተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች በነበሩ ግጭቶች ተፈናቅለው በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች የሚኖሩ ተፈናቃዮች አዲስን ዓመትን በቀያቸው በደስታ እና በፍቅር ይቀበሉ እንደነበበር ያስታውሳሉ። አሁን ያ ሁሉ ቀርቶ በመጠለያ ድንኳን ለማሳለፍ መገደዳቸውን ይናገራሉ። ሰላም እና ወደ ቀያቸው መመለስ የዓዲሱ ዓመት ተስፋ እና ምኞታቸው ነው።

https://p.dw.com/p/50LDP
በአማራ ክልል የጃራ መጠለያ ጣቢያ የሚገኙ ተፈናቃዮች
በአማራ ክልል የጃራ መጠለያ ጣቢያ የሚገኙ ተፈናቃዮችምስል፦ Alemenw Mekonnen/DW

የተፈናቃዮች የአዲስ ዓመት ምኞትና ተስፋ


ከተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች በነበሩ ግጭቶች ተፈናቅለውበአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች የሚኖሩ ተፈናቃዮች አዲስን ዓመትን በቀያቸው በናፍቆትና በፍቅር ሲቀበሉት እንደነበርና እንደወግና ባህላቸው ህፃናትን አዲስ ልብስ በማልበስ፣ ቀኑን ያደምቁ እንደነበር ዛሬ ላይ ሆነው ያስታውሳሉ፣ አሁን ያ ሁሉ ቀርቶ በመጠለያ ድንኳን ለማሳለፍ ተግድደዋል፣ በደቡብ ወሎ ዞን ጃሪና መካነ ሠላም፣ በሰሜን ወሎ ዞን ጃራ፣ በሰሜን ሸዋ ወይንሸት፣ በማዕከላዊ ጎንደር ዞን የቀበሮ ሜዳ፣ በሰሜን ጎንደር ዞን የደባርቅ መጠለያ ጣቢያዎች የሚገኙ ተፈናቃዮች በአዲሱ ዓመት ለኢትዮጵያ ያላቸውን መልካም ምኞትና ያላቸውን ተስፋ ለዶይቼ ቬሌ ገልፀዋል፡፡በአማራ ክልልከትግራይ፣ ከኦሮሚያና ከቤኒሻንጉል ክልሎች የተፈናቀሉ 640 ሺህ ያክል ተፈናቃዮች ይገኛሉ፡፡

ዓለምነው መኮነን
ማንተጋፍቶት ስለሺ